Lyrics

በቃላት ድርድር በሙዚቃ ቃና ስሜን ስታብራራ ነፍሴን ስታጣራ አየሁኝ ጥበብ ሰማሁኝ ዕውቀት ልናገር ልመስክር የዚህን ሰው ጽናት ቀልጦ እንደሚበራ ሻማ መብራት በሌለው ከተማ እየቀለጠ በራልኝ እየሞተ አኖረኝ ለሱስ ባለእዳው ነኝ ህይወት እንዳይሰለቸኝ ሲጨነቅ ሲጠበብ አይተኛም ቀን ከሌት ለደስታዬ ሲዋትት ካህንዬ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ ካህንዬ የነብሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ መሰንቆዉን ይዞ ከደጄ ሲጫወት ያድራል ሲያዜም በበገና በክራር ነፍሴን ሲያለመልም እንደ መልከጼዴቅ ካህን ክህነቱ ከዘመን ዘመን የዘላለም አይደለም ወይ የሰጠኝ ደስታ ከላይ ስወድ ስጠላ የማይተወኝ ለትንሽ ደስታው አመስጋኝ አንዲህ ያለ ሰው የሰው ምርጥ በጊዜ የማይለወጥ ካህንዬ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ ቃል ከአንደበቱ እንደውሃ ይፈሳል እንደ ጅረት ልብን የሚመረምር ጠልቆ የሚገባ ከአንጀት ሰምና ወርቁን ተናገር ቅኔ በለሱን ደርድር በጻድቅ ሰው ቃላት ነፍሴ ገባች ከገነት ጣዕሙን ዜማ ስታዜም ቃልን ከህይወት ስትቀምም ስጋዬን ለየህ ከነፍሴ አቆራረጥከኝ ከእስትንፋሴ ካህንዬ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ የነፍሴ አገልጋይ እንቅልፍ አትተኛም ወይ እንደ መልከጼዴቅ ካህን ክህነቱ ከዘመን ዘመን የዘላለም አይደለም ወይ የሰጠኝ ደስታ ከላይ ከላይ ከላይ ከላይ ከሰማይ ከላይ ከላይ ከላይ ከሰማይ ከሰማይ
Writer(s): Ejigayehu Shibabaw Lyrics powered by www.musixmatch.com
instagramSharePathic_arrow_out