Lyrics

ባልፍም ኖሬ ስለ እናት ምድሬ እሷናት ክብሬ ኸረ እኔስ አገሬ ባልፍም ኖሬ ስለ እናት ምድሬ እሷናት ክብሬ ኸረ እኔስ አገሬ ስንት የሞቱለሽ ለክብርሽ ዘብ አድረው አልፈው ሲነኩሽ ባህርሽን ተሻግረው የጀግኖች አገር ያዳም እግር አሻራ ፈለገ ጊዎን ያንች ስም ሲጠራ እንኳ ሠማይ ላይ ባንዲራሽን አይቶ ስምሽ ሲጠራ ማን ዝም ይላል ሠምቶ እንኳን ሠማይ ላይ ባንዲራሽን አይቶ ኢትዮጲያ ሲባል ማን ዝም ይላል ሰምቶ ኦሆሆ ሆሆ አ በቀስተ ዳመናሽ ሰማይ መቀነቱን ባንዲራሽን ታጥቆ አርማሽ የታተመ እንኳን ባለም መዳፍ በአርያም ታውቆ የተራሮች አናት ዘብ የቆመልሽ ቤት ያክሱማ ራስ ጦቢያ የፍጥረት በርነሽ የክብ አለም ምዕራፍ ዞሮ መጀመሪያ በሠማዩ ላይ ቢታይ ቀለም የሷ ነው እንጂ ሌላ አይደለም የመጪው ዘመን ፊት ናት መሪ ዛሬ አለም ቢላት ኋላ ቀሪ ተውኝ ይውጣልኝ ልጥራት ደጋግሜ ኢትዮጲያ ማለት ለኔ አይደል ወይ ሥሜ ቢጎል እንጀራው ከመሶቡ ላይ እናት በሌላ ይቀየራል ወይ ይዤ አላነሳም እጄን ከቀሚሷ እናት እኮ ናት ተስፋ አልቆርጥም በሷ የሷን ውለታ ከፍሎ ሳይጨርስው ኢትዮጵያ ሲባል አብሮ አይልም ወይ ሰው ኢትዮጵያ (ኢትዮጵያ) ሀገሬ (ሀገሬ) ኢትዮጵያ (ኢትዮጵያ) ሀገሬ (ሀገሬ) ባንቺ አይደል ወይ ክብሬ ባልፍም ኖሬ ስለ እናት ምድሬ እሷናት ክብሬ ኸረ እኔስ አገሬ ስንት የሞቱለሽ ለክብርሽ ዘብ አድረው አልፈው ሲነኩሽ ባህርሽን ተሻግረው የጀግኖች አገር ያዳም እግር አሻራ ፈለገ ጊዎን ያንች ስም ሲጠራ እንኳ ሠማይ ላይ ባንዲራሽን አይቶ ስምሽ ሲጠራ ማን ዝም ይላል ሠምቶ እንኳን ሠማይ ላይ ባንዲራሽን አይቶ ኢትዮጲያ ሲባል ማን ዝም ይላል ሰምቶ ኦሆሆ ሆሆ አ የሠላሞን ዕፅ ነሽ የቅዱሳን ዕንባ ያበቀለሽ ቅጠል ዛሬ አዲስ አይደለም በለኮስው እሳት የነካሽ ሲቃጠል ሳይወስን ዝናሽ በቅርሦችሽ ድርሳን ባድባራት ታሪኩ ነብይ አይተው ከሩቅ ያሉልሽ በመፅሀፍ ኢትዮጲያን አትንኩ በሠማዩ ላይ ቢታይ ቀለም የሷ ነው እንጂ ሌላ አይደለም የመጪው ዘመን ፊት ናት መሪ ዛሬ አለም ቢላት ኋላ ቀሪ ተውኝ ይውጣልኝ ልጥራት ደጋግሜ ኢትዮጲያ ማለት ለኔ አይደል ወይ ሥሜ ቢጎል እንጀራው ከመሶቡ ላይ እናት በሌላ ይቀየራል ወይ ይዤ አላነሳም እጄን ከቀሚሷ እናት እኮ ናት ተስፋ አልቆርጥም በሷ የሷን ውለታ ከፍሎ ሳይጨርስው ኢትዮጵያ ሲባል አብሮ አይልም ወይ ሰው ኢትዮጵያ (ኢትዮጵያ) ሀገሬ (ሀገሬ) ኢትዮጵያ (ኢትዮጵያ) ሀገሬ (ሀገሬ) ባንቺ አይደል ወይ ክብሬ ባልፍም ኖሬ ስለ እናት ምድሬ እሷናት ክብሬ ኸረ እኔስ አገሬ በሰሜን በደቡብ በምስራቅ በምዕራብ ላይ ሙሉ ይሁን ያንቺ ሲሳይ በሰሜን በደቡብ በምስራቅ በምዕራብ ላይ ሙሉ ይሁን ያንቺ ሲሳይ (ይራቅ ይራቅ) ችግር ከምድርሽ (ሙሉ ሙሉ) ይሁን ሲሳይሽ (ይራቅ ይራቅ) ችግር ከምድርሽ (ሙሉ ሙሉ) ይሁን ሲሳይሽ (ይራቅ ይራቅ) አይ ሙሉ (ሙሉ ሙሉ) ወይ ሙሉ (ሙሉ ሙሉ) አይ ሙሉ (ሙሉ ሙሉ) ወይ ሙሉ (ሙሉ ሙሉ) አይ ሙሉ (ይራቅ ይራቅ) ወይ ሙሉ (ሙሉ ሙሉ) አይ ሙሉ (ይራቅ ይራቅ) ወይ ሙሉ (ሙሉ ሙሉ)
Writer(s): Teddy Afro Lyrics powered by www.musixmatch.com
instagramSharePathic_arrow_out